ሕግ-ነክ

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች፡ ቅፅ 5

ሕግ-ነክ ሰነዶች/ MIRH/ 12 ሐምሌ 2014

የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር 454/97 አንቀጽ 2/1/ ሥር የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከአምስት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የሚሠጠው የሕግ ትርጉም በየትኛውም ደረጃ ላይ በሚገኝ የፌደራል ወይም የክልል ፍርድ ቤት ላይ አስገዳጅነት ይኖረዋል ተብሎ በመደንገጉ ፍርድ ቤቶች የሰበር ችሎቱ የሰጠውን የሕግ ትርጉም ተከትለው እንዲሰሩ ለማስቻል ነው፡፡

በየፍርድ ቤቶች ለተመሳሳይ ጉዳዮች ይሰጥ የነበረውን የተለያዩ ውሳኔዎች በማስቀረት የፍርድ ቤቶች ውሳኔዎች ወጥነት እንዲኖራቸውና ተገማችም እንዲሆኑ ከማድረግ አኳያ ጠቀሜታው ከፍተኛ በመሆኑም ነው፡፡

በሌላ በኩል ውሳኔዎቹ በጥራዝ መልክ መዘጋጀታቸው ጥናትና ምርምር ለሚያካሂዱ የሕግ ተማሪዎችና ምሁራን፣ ለጠበቆችና ለሕብረተሰቡ በአጠቃላይ ውሳኔዎቹን በቀላሉ ለማግኘት ያስችላል፡፡

 

ዝርዝሩን ያንብቡ፡

federal-supreme-court-decisions-volume-5 

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማትና አስተዳር ቢሮ የመንግስት ቤቶች አስተዳደር መመሪያ

Previous article

የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓት እና የማስረጃ ሕግ

Next article

You may also like

Comments

Leave a reply