Handcuffed hands of arrested criminal man in black shirt and handcuffs
ሕግ-ነክ

የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓት እና የማስረጃ ሕግ

ሕግ-ነክ ሰነዶች/ MIRH/ 12 ሐምሌ 2014

ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት እና ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ጋር የተጣጣመና መርሆቻቸውንና እሴቶቻቸውን ለማስፈጸም የሚያስችል ዘመናዊ የወንጀል ፍትህ ሂደት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤

በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ሥርዐት የወንጀል ፍርድ ሂደት የተጠርጣሪን እና የተከሳሽን እንዲሁም የወንጀል ተጎጅዎችን ሰብዓዊ መብቶችን ለማክበርና ለማስከበር፣ የሕግ የበላይነትን ለማስፈን የሚያስችል ወጥ እና የተሟላ ሕግ ማውጣት በማስፈለጉ፣ ሀገሪቱ በወንጀል ፍትሕ ሥርዐት በዓለም አቀፍ ሕግ ያሏትን መብቶች ለማስከበርና የተጣሉባትን ግዴታዎች ለመወጣት የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ በማስፈለጉ፤

የወንጀል ፍትህ አስተዳደሩ ለጠቅላላው ጥቅም እንዲሰራ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑና የወንጀል ክርክር የሚመራበትን የሥነ-ሥርዐትና የማስረጃ ድንጋጌ ወጥና አካታች በሆነ መልኩ እንደገና ማደራጀት በማስፈለጉ፣ እና በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ ፶፭ (፩) እና ፶፭ (፭) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡

 

ሰነድ፡

የወንጀል ሕግ ሥነ -ሥርዓት እና የማስረጃ ሕግ

 

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች፡ ቅፅ 5

Previous article

የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ የሚያስገኙ ስራዎች ምዝገባ

Next article

You may also like

Comments

Leave a reply