መመሪያዎች/ MIRH/ 24 መስከረም 2015
በ-የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በማቋቋሚያ አዋጅ ቁ. 1133/2011 አንቀጽ 8 ንዑስ አንቀጽ (1) እና በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነምግባር አዋጅ ቁ. 1162/2011 አንቀጽ 23 ንዑስ አንቀጽ (2)፣ አንቀጽ 56 ንዑስ አንቀጽ (6)፣ አንቀጽ 61 ንዑስ አንቀጽ (7) እንዲሁም አንቀጽ 163 ንዑስ አንቀጽ (2) በተሰጠው ስልጣን መሠረት ይህንን መመሪያ አውጥቷል።
የዚህ መመሪያ ዓላማ የምርጫ ማስፈጸሚያ ቁሳቁሶችና ሰነዶች ለሚመለከተው የምርጫ አስፈጻሚ አካል በአግባቡ የሚጓጓዙበትን፣ ርክክብ የሚደረግበትን፣ በወቅቱ የሚሰራጭበትን፣ ጥቅም ላይ የሚውሉበትን፣ ወደ ቦርዱ የሚመለሱበትን እና የሚወገዱበትን ግልጽ የሆነ የአሰራር ስርዓት መዘርጋት ነው።
ሰነድ፡
የምርጫ ማስፈጸሚያ ቁሳቁሶችና እና ሰነዶች ድልድል፣ ሥርጭት፣ አጠቃቀም፣ ርክክብና አወጋገድ መመሪያ ቁጥር 8 2013
Comments