የምስል ወድምፅ ቅንብሮች

በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ሥነ-ተግባቦት ተማሪዎች ስለሚራህ (MIRH) የመረጃ ቋት አጠቃቀምና ተሳትፎ ገለጻና ውይይት

MIRH/ባህር ዳር/የካቲት 9፣ 2015

የኢትዮጵያ ናሽናል ሚዲያ ሳፖርት (ENMS) ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ሥነ-ተግባቦት ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር (Media, Information and Research Hub-MIRH) የመረጃ ቋት ምንነት፣ አጠቃቀም፣ የጽሑፍ ተሳትፎ እና ሌሎች እድሎችን በተመለከተ ከትምህርት ክፍሉ መምህራን እና ተማሪዎች ጋር ሰፊ ገለጻና ውይይት ተደርጓል፡፡
ገለጻውን የሰጡት የኢትዮጵያ ናሽናል ሚዲያ ሳፖርት (ENMS) መሥራች እና ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር አቶ ፍቃዱ ዓለሙ ሲሆኑ የትምህርት ክፍሉ ተማሪዎች በሚራህ የመረጃ ቋት ስለሚያገኙት ጥቅም፣ የበጎ ፈቃድ ተሳትፎ፣ ልዩ ልዩ ጽሑፎችን አስመልክቶ ሰፊ ገለጻና ውይይት ሰጥተዋል፡፡
የትምህርት ክፍሉ ተማሪዎች በበኩላቸው ስለሚራህ MIRH የመረጃ ቋት አጠቃቀም የተደረገው ገለጻ እንዳስደሰታቸው እና ወደ ፊት በመረጃ ቋቱ ልዩ ልዩ ጽሑፎችን ለማበርከት ፈቃደኛ መሆናቸውን አንዳንድ ተማሪዎች በጥያቄና መልስ ውይይቱ ላይ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ናሽናል ሚዲያ ሳፖርት (ENMS) የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ የጋዜጠኝነት እና ተግባቦት ትምህርት ክፍሉ ሓላፊ አቶ ሰሎሞን ሙሉን ጨምሮ እና ሌሎች አስተባባሪዎችን ስላደረጉት ትብብር ምስጋና ያቀርባል፡፡

በዐዲስ አበባ ከተማ እና አካባቢው በሥርጭት ላይ የሚገኙ ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያዎች እነማን ናቸው?

Previous article

“የኢትዮጵያ ሚዲያ ግጭት አገናዛቢነት እና የሰላም ግንባታ” በሚል ሲካሄድ የቆየው ውይይት ባለ13 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል

Next article

You may also like

Comments

Comments are closed.