መመሪያዎች

ሥርዓተ-ጾታን ያገናዘበ የግጭት አዘጋገብ መመሪያ ለመገናኛ ብዙኅን

የግጭት አዘጋገብ መመሪያ /  MIRH/ 03 የካቲት 2014
አዘጋጅ፡ የኢትዮጵያ ሚዲያ ባለሥልጣን በተ.መ.ድ የሥርዓተ-ፆታ እኩልነትና ሴቶችን የማብቃት ክፍል (UN Women) ጋር በመተባበር
መግቢያ 

ይህ መመሪያ በኢትዮጵያ ሚዲያ ባለሥልጣን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (..) የሥርዓተፆታ እኩልነትና ሴቶችን የማብቃት ክፍል (UN Women) ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን ጋዜጠኞች በግጭት ወቅት የሥርዓተ ፆታ ጉዳዮችን ለማካተት መከተል ስለሚገባቸው መርሆዎች በዝርዝር የያዘ መመሪያ ነው። በተጨማሪም መመሪያው መገናኝ ብዙሃን በግጭት ዘገባ ወቅት ወይም ደግሞ በመደበኛው ጊዜ ስለሴቶች በትክክለኛው መልኩ እንዴት መዘገብ እንዳለባቸው በጥልቀት ያስረዳል፡፡ በተለይ በዘገባዎቻቸው ወቅት ማከናወን ስለሚገባቸው ተግባራት እና ሊያጋጥሟቸው ስለሚችሉ ተግዳሮቶችና መፍትሔዎቻቸው ያትታል፡፡ በአጠቃላይ ይህሥርዓተ ፆታን ያገናዘበ የግጭት ወቅት ዘገባ መመሪያ ጋዜጠኞች በግጭት ወቅት በተቻለ መጠን ትክክለኛ ዘገባ እንዲሠሩ እገዛ ለማድረግ ታልሞ የተዘጋጀ ነው።

የዚህ መመሪያ ዓላማ ምንድን ነው? 

ይህ መመሪያ ጋዜጠኞች ግጭት ተኮር ዘገባ በሚያዘጋጁበት ጊዜ ሴቶች እና ወንዶችን በተገቢው ሁኔታ እና የጋዜጠኝነት ሥነምግባር በተሞላበት መልኩ እንዲያቀርቡ እና እንዲወክሉ ለማገዝ ያለመ ነው። እንዲሁም መመሪያው የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ከግጭት ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ዘገባዎች በሚያጠናቅሩበት ጊዜ ስርአተፆታ ላይ የተመረኮዙ ጅምላ ፍርጃዎችን፣ የተዛቡ ስርአተፆታዊ አስተሳሰቦችን እና ስርዓተፆታዊ አድልዎችን መቀነስ እንዲችሉ እገዛ ያደርጋል። በተጨማሪም ሥርዓተፆታን ያማከለ የግጭት ዘገባ ምንነት እና አስፈላጊነት እንዲሁም ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉ የግጭት ዘገባ አቀራረቦችን ለመቀነስ የሚያስችሉ ጠቃሚ ማብራሪያዎችን ይሰጣል።

 

ሙሉውን መመሪያ ከዚህ በታች ማግኘት ይችላሉ፡፡ 

የዜና ጉዳይ መረጣ እና ምዘና 

Previous article

የምስል ወድምፅ ቅንብሮች

Next article

You may also like

Comments

Comments are closed.