ሚራህ (MIRH) ምንድን ነው?
ሚራህ በቀጥታ ከእንግሊዘኛው ሥያሜ የተወሰደ ምሕጻረ-ቃል ሲሆን፤ የሚዲያ፣ ኢንፎርሜሽን እና ምርምር ቋት (Media Information and Research Hub-MIRH) ማለት ነው።
ይህ ሚዲያ የዲጂታል ማዕከል የሀገር ውስጥ የመገናኛ ብዙኀን ታሪክ፣ መረጃ፣ እድገት፣ ልዩ ልዩ የሚዲያና የኮሙዩኒኬሽን የጥናት ውጤቶች፣ የጋዜጠኞች ግለ-ታሪክ፣ የሙያ ልምዶች፣ የመገናኛ ብዙኀንና ጋዜጠኝነት ሙያዊ ማብራሪያ ሰነዶች እና ሌሎች ኹነኛ መረጃዎችን በአንድ ቦታ፤ በአንድ ጊዜ የሚገኙበት የመረጃ ቋት ነው፡፡
ሚራህ (MIRH) ከፎዮ የሚዲያ ማዕከል (Fojo-IMS በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በኢትዮጵያ ናሽናል ሚዲያ ሳፖርት (ENMS) እየተተገበረ ያለ ፕሮጀክት ሲሆን የኢትዮጵያ ሚዲያ ካውንስል (Ethiopian Media Council)፣ የኢትዮጵያ ሴት የሚዲያ ሙያተኞች ማኅበር (Ethiopian Media Women Association - EMWA)፣ የኢትዮጵያ አርታኢያን ማኅበር (Editors Guild - EG)፣ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ራዲዮ አሠራጮች ማኅበር (Ethiopian Community Radio Broadcaster Association - ECRBA) እና የኢትዮጵያ ብሮካስተሮች ማኅበር (Association of Ethiopian Broadcasters - AEB) አብረውት ይሠራሉ፡፡
Follow:
ሕግ-ነክ
በአዲሱ የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ህግ የተለወጡ ዋና ዋና ጉዳዮች
ሕግ-ነክ ሰነዶች/ MIRH/ 24 መስከረም 2015 በ- የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በአዲሱ ...
ሕግ-ነክ
የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነምግባር አዋጅ
ሕግ-ነክ ሰነዶች/ MIRH/ 24 መስከረም 2015 በ- የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ኢትዮጵያዊያን ...